|
|
|
|
|
|
عهد جدید
|
|
|
|
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (Selassie) 1962
|
|
|
|
۱ |
ከመኰንን ጋር ለመብላት በተቀመጥህ ጊዜ፥ በፊትህ ያለውን በደኅና አስተውል፤ |
۲ |
ሰውነትህም ቢሳሳ፥ በጕሮሮህ ላይ ካራ አድርግ። |
۳ |
ጣፋጩ መብል አይመርህ የሐሰት እንጀራ ነውና። |
۴ |
ባለጠጋ ለመሆን አትድከም፤ የገዛ ራስህን ማስተዋል ተው። |
۵ |
በእርሱ ላይ ዓይንህን ብታዘወትርበት ይጠፋል፤ ባለጠግነት ወደ ሰማይ እንደሚበርር እንደ ንስር ለራሱ ክንፍ ያበጃልና። |
۶ |
የቀናተኛን ሰው እንጀራ አትብላ፥ ጣፋጩ መብልም አይመርህ፤ |
۷ |
በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ ብላ ጠጣ ይልሃል፥ ልቡ ግን ካንተ ጋር አይደለም። |
۸ |
የበላኸውን መብል ትተፋዋለህ፥ ያማረውንም ቃልህን ታጠፋዋለህ። |
۹ |
በሰነፍ ጆሮ አንዳች አትናገር፥ የቃልህን ጥበብ ያፌዝብሃልና። |
۱۰ |
የቀድሞውን የድንበር ምልክት አታፍልስ፤ ወደ ድሀ አደጎች እርሻ አትግባ፤ |
۱۱ |
ታዳጊአቸው ጽኑ ነውና፥ እርሱም ፍርዳቸውን ከአንተ ጋር ይፋረዳልና። |
۱۲ |
ልብህን ለተግሣጽ ስጥ፥ ጆሮህንም ወደ እውቀት ቃል። |
۱۳ |
ሕፃንን ከመቅጣት ቸል አትበል፥ በበትር ብትመታው አይሞትምና። |
۱۴ |
በበትር ትመታዋለህ፥ ነፍሱንም ትታደጋለህ። |
۱۵ |
ልጄ ሆይ፥ ልብህ ጠቢብ ቢሆን ልቤ ደግሞ ደስ ይለዋል፤ |
۱۶ |
ከንፈሮችህም በቅን ቢናገሩ ኵላሊቶቼ ደስ ይላቸዋል። |
۱۷ |
ልብህ በኃጢአተኞች አይቅና፤ ነገር ግን ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር፤ |
۱۸ |
በእውነት ፍጻሜ አለህና፥ ተስፋህም አይጠፋምና። |
۱۹ |
ልጄ ሆይ፥ ስማ ጠቢብም ሁን ልብህንም በቀናው መንገድ ምራ። |
۲۰ |
የወይን ጠጅ ከሚጠጡ ጋር አትቀመጥ ለሥጋም ከሚሣሡ ጋር፤ |
۲۱ |
ሰካርና ሆዳም ይደኸያሉና፥ የእንቅልፍም ብዛት የተቦጫጨቀ ጨርቅ ያስለብሳልና። |
۲۲ |
የወለደህን አባትህን ስማ፥ እናትህም ባረጀች ጊዜ አትናቃት። |
۲۳ |
እውነትን ግዛ አትሽጣትም፥ ጥበብን ተግሣጽን ማስተዋልንም። |
۲۴ |
የጻድቅ አባት እጅግ ደስ ይለዋል፥ ጠቢብንም ልጅ የወለደ ሐሤትን ያገኛል። |
۲۵ |
አባትህና እናትህ ደስ ይበላቸው፥ አንተንም የወለደች ደስ ይበላት። |
۲۶ |
ልጄ ሆይ፥ ልብህን ስጠኝ፥ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ፤ |
۲۷ |
ጋለሞታ ሴት የጠለቀች ዐዘቅት ናትና፥ ሌላይቱም ሴት የጠበበች ጕድጓድ ናትና። |
۲۸ |
እንደ ሌባ ታደባለች ወስላቶችንም በሰው ልጆች መካከል ታበዛለች። |
۲۹ |
ዋይታ ለማን ነው? ኀዘን ለማን ነው? ጠብ ለማን ነው? ጩኸት ለማን ነው? ያለ ምክንያት መቍሰል ለማን ነው? የዓይን ቅላት ለማን ነው? |
۳۰ |
የወይን ጠጅ በመጠጣት ለሚዘገዩ አይደለምን? የተደባለቀ የወይንን ጠጅ ይፈትኑ ዘንድ ለሚከተሉ አይደለምን? |
۳۱ |
ወደ ወይን ጠጅ አትመልከት በቀላ ጊዜ፥ መልኩም በብርሌ ባንጸባረቀ ጊዜ፥ እየጣፈጠም በገባ ጊዜ። |
۳۲ |
በኋላ እንደ እባብ ይነድፋል፥ እንደ እፉኝትም መርዙን ያፈስሳል። |
۳۳ |
ዓይኖችህ ጋለሞታዎችን ያያሉ፥ ልብህም ጠማማ ነገርን ይናገራል። |
۳۴ |
በባሕር ውስጥ እንደ ተኛ ትሆናለህ፥ በደቀልም ላይ እንደ ተኛ። |
۳۵ |
መቱኝ፥ ያውም አልተሰማኝም፤ ጐሰሙኝ፥ አላወቅሁምም። መቼ እነሣለሁ? ደግሞ ጨምሬ እሻታለሁ ትላለህ። |
Persian Dari 2007 |
Dari Bible (Today’s Dari Version 2008) © |